
ነይልን(2) ካለንበት
ከሰማያት በላይ ካለው ከማደሪያሽ(2)
ዝማሬ ከሞላው ከዘላለም ቤትሽ
የምድር ፍትረታት ማርያም ማርያም ሲሉሽ(2)
የቃል እናት እመቤቴ ነይ በሰረገላሽ(2)
አዝ........................
ከፀጥታ ወደብ ከፍቅር አውድማ(2)
ከሰላሙ መንደር ከእውነት ከተማ
ሰዓሊ ለነ ቅድስት ውዳሴሽ ሲሰማ(2)
ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር ነይልን ከራማ(2)
አዝ.....................
ዘርፋፋው ቀሚስሽ ይውረድ ከሰማያት(2)
ዕንባችን ይታበስ በአንቺ አማላጅነት
የጽዮን ዝማሬ ተሞላች ነፍሳችን(2)
ንዒ (3) እንበል እንደ አባቶቻችን(2)
አዝ........................
ፍጥረታት ሊድኑ በአማላጅነትሽ(2)
የዘላለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሽ
ትውልድ ይህን አምኖ ብፅዕት ይልሻል(2)
እናቴ መመኪያዪ ምርኩዜ ሆነሻል(2)
አዝ.......................
የልብን ሲያዋዩሽ ሰምተሽ ዝም አትይም (2)
ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም
ከአይን ጥቅሻ ፈጥነሽ ትደርሽለታለሽ(2)
ከሐዘን ከመከራ ታሳርፊዋለሽ(2)
አዝ.........................