
ሳማ ሰንበት በኢትዮጵያ ውስጥ ብቸኛው ፅላተ እግዚእነ ሰንበት (የሰንበት ፅላት) ያለበት በአመት አንዴ ብቻ በአለ ንግሱ የሚከበር የ300 ዓመት ታሪክ ያለው ገዳም ነው፡፡ ይህም ገዳም በንጉስ ሣህለ ስላሴ (የአፄ ምንሊክ አያት) በአንድ የበቁ አባት መሪነት እና ጥቆማ እንደተገደመች ታሪክ ይነግረናል፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ይህችን ቀን በአብይ ፆም እኩሌታ ደብረ ዘይት ብላ ሳምንቱን ሰይማ የጌታ ምፅአት የሆነችውን የሰንበትን እለት እያሰበች በአመት አንዴ ይህችን የጌታ መምጫ ቀን ትዘክራለች፡፡